ፌዴራል ፖሊስ በስብሰባ ተወጥሯል፤ የሚክዱ አባላት ቁጥር ጨምሯል

federalበአዲስ አበባ ተደርጎ ያልተሳከው እና የአዛዦች የእርስበርስ ግጭትን ጨምሮ የተጠናቀቀው የፌዴራል ፖሊስ ስብሰባ በባህር ዳር በድጋሚ ተደርጓል፡፡ ስብሰባው የተከወነው ከየካቲት 13-16 ሲሆን ይኽም እንደ አዲስ አበባው ስብሰባ በግጭት እና በጭቅጭቅ ታጅቦ ያለ ውጤት ተበትኗል፡፡ በስብሰባዎቹ ላይ ህዝባዊ ቁጣዎች በስፋት የተነሱ ሲሆን፤ “ህዝቡ መንግስትን ለምን ጠላው? መንግስት ህዝብን ለምን ያሰቃያል? ለምን ህዝባችንን ግደሉ እንባላለን? ወደ ህዝባችን እንድንተኩስ ለምን እንታዘዛለን?” የሚሉ ጥያቄዎች እየተነሱ ዱላ ቀረሽ ጭቅጭቅን ፈጥረዋል፡፡

በአዋሳ በተማሪዎች ላይ የሕወሃት ሰራዊት ተኩስ እንደከፈተ ተዘገበ

በሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ዋናው ካምፓስ ዉስጥ የሕወሃት ታጣቂዎች በተማሪዎች ላይ ተኩስ እንደከፈቱ የደረሰን ዘገባ ያመለክታል። በዩኒቨርሲቲ ዛሬ ትምህርት ያልነበረ ሲሆን፣ በርካታ ፌዴራል ፖሊሶች ካምፓሱን ተቆጣጥረዉታል። ጩኸትና ረብሻም ተሰምቷል።