አነጋጋሪው የአርቲስት ሜሮን ጌትነት ግጥም

“ሀገሬ”
ልክ ነበርክ አንተ
እዚህ ለፍተህ ስትኖር ባገርህ አፈር ላይ
‘አባን ከና’ የሚል ያንተን ልፋት የሚያይ
አንዳችም ሰው የለም ህዝቡ ውጭ አምልኳል
ልቡ ተንበርክኳል
ላገር ስታነባ በጥቅም ይለካል
በነጻ ያላበህ በዶራል ይተካል
አሁን በቀደም ለት
ለቤታችን ምርጊት ያቦካናት ጭቃ
ብሎኬት ለማቆም ቦታው ተፈልጎ ተጣለች
ተዝቃ
ተመስገን ማለት ነው ቀርቶ መማረሩ
ስንዝር መቀበሪያም ካልጠፋ ባገሩ
ተመስገን ነው ጥሩ
ለኑሮማ ሚሆን መሬት ማን አሲዞን
ቤታችን ወደ ላይ ቢቀርበን እግዜሩ
ወደላይ ነው ጥሩ
ወደ ላይ ወደ ላይ ወደላይ አሻቅቦ
አ ንደኛው ባንዱላይ ኑሮውን ደርቦ
……ህ…….. ም……….