ፌዴራል ፖሊስ በስብሰባ ተወጥሯል፤ የሚክዱ አባላት ቁጥር ጨምሯል

federalበአዲስ አበባ ተደርጎ ያልተሳከው እና የአዛዦች የእርስበርስ ግጭትን ጨምሮ የተጠናቀቀው የፌዴራል ፖሊስ ስብሰባ በባህር ዳር በድጋሚ ተደርጓል፡፡ ስብሰባው የተከወነው ከየካቲት 13-16 ሲሆን ይኽም እንደ አዲስ አበባው ስብሰባ በግጭት እና በጭቅጭቅ ታጅቦ ያለ ውጤት ተበትኗል፡፡ በስብሰባዎቹ ላይ ህዝባዊ ቁጣዎች በስፋት የተነሱ ሲሆን፤ “ህዝቡ መንግስትን ለምን ጠላው? መንግስት ህዝብን ለምን ያሰቃያል? ለምን ህዝባችንን ግደሉ እንባላለን? ወደ ህዝባችን እንድንተኩስ ለምን እንታዘዛለን?” የሚሉ ጥያቄዎች እየተነሱ ዱላ ቀረሽ ጭቅጭቅን ፈጥረዋል፡፡

አነጋጋሪው የአርቲስት ሜሮን ጌትነት ግጥም

“ሀገሬ”
ልክ ነበርክ አንተ
እዚህ ለፍተህ ስትኖር ባገርህ አፈር ላይ
‘አባን ከና’ የሚል ያንተን ልፋት የሚያይ
አንዳችም ሰው የለም ህዝቡ ውጭ አምልኳል
ልቡ ተንበርክኳል
ላገር ስታነባ በጥቅም ይለካል
በነጻ ያላበህ በዶራል ይተካል
አሁን በቀደም ለት
ለቤታችን ምርጊት ያቦካናት ጭቃ
ብሎኬት ለማቆም ቦታው ተፈልጎ ተጣለች
ተዝቃ
ተመስገን ማለት ነው ቀርቶ መማረሩ
ስንዝር መቀበሪያም ካልጠፋ ባገሩ
ተመስገን ነው ጥሩ
ለኑሮማ ሚሆን መሬት ማን አሲዞን
ቤታችን ወደ ላይ ቢቀርበን እግዜሩ
ወደላይ ነው ጥሩ
ወደ ላይ ወደ ላይ ወደላይ አሻቅቦ
አ ንደኛው ባንዱላይ ኑሮውን ደርቦ
……ህ…….. ም……….

ኤርሚያስ ለገሰ – ለዲያቆን ዳንኤል ክብረት ( የመጨረሻ አስተያየት)

ermias_legeseለዲያቆን ዳንኤል ክብረት ( የመጨረሻ አስተያየት)
በመጀመሪያ ጊዜህን ሰጥተህ የጠየኩትን መረጃ ስለሰጠኸኝ ምሥጋናዬ ይድረስህ። በተደጋጋሚ እንደገጵኩት የአንተን የድምጵ መልእክት የሰማሁት ማስታወሻውን ከመጻፌ በፊት በማህበራዊ ድረገጾች በሰፊው እየተራገበ በመመልከቴ ነው። አንተ እኔን ለመወረፍ እንደሞከርከው ” ጊዜና ሁኔታ ያላገናዘበ” ሳይሆን አጀንዳውን ጐትተው ወደ መድረክ ያመጡት ወቅታዊ በመሆኑ ነው።
ከአንዳንድ ወዳጆቼ ጋር በነበረን ምልልስ እንደገለፅኩት ይህን ሰነድ ወደ ፊት ይዞ መምጣት አሁን የሚደረገውን የኢትየጵያ ሙስሊሞች የነፃነት ትግል ጥላሸት ለመቀባትና ለመቀልበስ በማሰብ ነው። ባጭሩ ያቀረብከው ሰነድ መቼም ይሁን መቼ ” ጊዜውን እየጠበቀ የሚፈነዳ ፈንጂ” መሆኑን አስምሬበታለሁ። አሁንም እምነቴ ይህ ነው።
በዝርዝር ካነሳሀቸው ጉዳዬች አንዳንዶቹን ነቅሼ በማውጣት ነጥብ በነጥብ አስተያየት ልስጥበት፣

ዲ/ን ዳንኤል ክብረት ለአቶ ኤርሚያስ ለገሰ የሰጠው ምላሽ

daniel“ቢሮህ አስጠርተህን ቤተ ክርስቲያኒቱንና የፈረደበትን አማራ ምን ብለህ እንደተሳደብክ የምናውቀው አንተ እና እኛ ነን፡፡”ኤርምያስ ኤርምያስ ሆይ!የኤርምያስ ለገሠን ‹ግልጽ ደብዳቤ› አነበብኩት፡፡ አንብቤው በሁለት ምክንያት ሳልጽፍለት ዘገየሁ፡፡ በአንድ በኩል ስለ ኤርምያስ ከነበረኝ የዋሕ ግምት የተነሣ ኤርምያስን ያህል ሰው ይህን ያህል አይሳሳትምና በቀጣዮቹ ቀናት በስሜ የወጣ ጽሑፍ ነው እንጂ የጻፍኩት እኔ አይደለሁም ይል ይሆናል ብዬ በመገመት፡፡ጽሑፉ እንደወጣ ብዙ ሰዎች አሁን እኔ የምነግርህን ሲገልጡት ነበርና ትሰማቸዋለህ ብዬ አስቤ ነበር፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ የሐዲስ ዓለማየሁ የባሕል ማዕከል ባዘጋጀው ዐውደ ጥናት ላይ ልካፈል ወደ ደብረ ማርቆስ ተጉዤ ስነበር፡፡

ማስተርስ/ዶክተሬት እንደ መለዋወጫ እቃ!

hatታሪኩ አባዳማ | የካቲት 2007 ልጄ አስራ ሁለተኛ ክፍል ስለጨረሰ የደስታዬ ተካፋይ ትሆኑ ዘንድ… የሚል ግብዣ ደርሷችሁ አያውቅም? እናንተም ፋሽኮ ቪኖ ወይንም እናትና ልጅ አረቄ ይዛችሁ ድግሱን ለማድመቅ ሳትሄዱ አልቀራችሁም – የዚያን ዕለት ጎረምሶቹ የቀለጠ ፓርቲ ደግሰው እስኪነጋ ይጨፍራሉ አሉ… ይህስ ይሁን።እንድህረ ምረቃ ፕሮግራም ላይ መሆኑን አንድም ቀን ሲናገር ሰምታችሁ የማታውቁት በቅርብ የምታውቁት ሰው ፣እንዲያውም በመደበኛ ትምህርት ከስንተኛ ክፍል ነበር? አቋርጦ ወደ ሄደበት ሄዶ (ጫካ ወይንም ምርኮ) ግን የዛሬ ‘ሹም’ ‘የማስተርስ ፣ ዶክትሬት ዲግሬዬ በፖሰታ ስለደረሰኝ የደስታዬ ተካፋይ እንድትሆን ብሎ ቢጠራችሁስ? ይኼ ሰው ድሮ ትምህርት ቤት የተመዘገበበት ስም ሌላ ነበር… አሁን ደግሞ አዲስ ስም ብቻ ሳይሆን አዲስ ማዕረግ ፣ አዲስ ቤት ፣ አዲስ መኪና… ምኑ ቅጡ… ባናቱ ላይ ዲግሪ ሸምቶበታል።